Posts

ማሊያዊው የፊት እና የመስመር አጥቂ አማራ ማሌ አዲሱ ፈረሰኛ ለመሆን ተቃርቧል።

Image
በአሁኑ ሰዓት በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ውስጥ በሙከራ ላይ ከሚገኙት 3 ተጨዋቾች መካከል የማሊ ዜግነት ያለው አማራ   ማሌ   የቅዱስ ጊዮርጊስ አሰልጣኞችን ማሳመን እንደቻለ የፈረሰኞቹ ገጽ ታማኝ የመረጃ ምንጮች አሳውቀውናል። ይህ የፊት   እና የመስመር አጥቂ ተጨዋች በልምምድ ሜዳ እያሳየ ካለው ብቃት መነሻነት   የክለቡ አሰልጣኞች በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ እና በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ላይ ተጨዋቹ ቅዱስ ጊዮርጊስን ይጠቅማል ብለው በማመናቸው  በቀጣይ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ይፈርማል ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ተጨዋች መጪውን አዲስ አመት በማስመልከት በቀጣይ ቀናት ወደ ማሊ የሚጓዝ ሲሆን አዲስ አመትን በአገሩ አሳልፎ ወደ አዲስ አበባ ሲመለስ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር   ኮንትራት ይፈራረማል ተብሎ እንደሚጠበቅ   ምንጮቻችን ያደረሱን መረጃ ያሳያል፡፡  አማራ   ማሌ   በማሊ እግርኳስ ክለብ ታሪክ ታላላቅ ስም ባላቸው ክለቦች ውስጥ ያለፈ ተጨዋች ነው። በአሁኑ ወቅት በማሊ ታላቅ ክለብ የሆነው የስታድ ማሊ ክለብ ተጨዋች ሲሆን 1 ሜትር ከ 82 ሳንቲሜትር ይረዝማል። ይህ ተጨዋች በማሊ ዋና ከተማ ባማኮ ታህሳስ 5 ቀን 1982 እንደተወለደ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። ተጨዋቹ 25 ዓመቱ ሲሆን በሁለቱም እግሮቹ ኳስ መጫወት የሚችል  ተጨዋች ነው ፡፡ በ አ ከ 2009-2012 የማሊ ክለብ ለሆነው ባማኮ፣ 2013-2015 ለጆሊባ እንዲሁም በ 2016 ወደ ጊኒ ተጉዞ...

የፈረሰኞቹ ገጽ በነገው ዕለት!

Image
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ8ኛ ሳምንት መርኃ ግብሮች ከመጪው ቅዳሜ አንስቶ ይካሄዳሉ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ የ9ኛ ሳምንት መርኃ ግብሩን ከመከላከያ ጋር ቅዳሜ በ10 ሰዓት ያከናውናል፡፡ ይህንን ጨዋታ በማስመልከት በነገው ዕለት በተለመደው መልኩ የቅድመ ጨዋታ ዳሠሳን ከፈረሰኞቹ ገጽ ይጠብቁ! የሁለቱ ክለቦች ያሳለፍነው ዓመት ግንኙነት፣ ያሳለፍነው ዓመት ጨዋታ እና እውነታዎች፣ የሁለቱ ክለቦች ቁጥራዊ መረጃዎች፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚ የሆነው መከላከያ የጨዋታ አቀራረብ እና የጨዋታ ዕቅዶች በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ ቋንቋ ይቀርባሉ፡፡ የፈረሰኞቹ ገጽ!

የቅዱስ ጊዮርጊስ ዝማሬዎችን በቀጭኑ ሽቦ!

Image
እኛ ቅዱስ ጊዮርጊሳውያን ክለባችንን ባገኘበው መንገድ ሁሉ ለማስተዋወቅ አንሰንፍም፡፡ ስለ ክለባችን ለመናገር አንቦዝንም፡፡ የዕለት ተዕለት ጉዟችን ውስጥ ክለባችን አለ፡፡ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ ዛሬ ጊዮርጊስን የምናስተዋውቅበት አማራጮችን በአንድ አሳድገናል፡፡ ስለ እግርኳስ ለሚያውቁት ብቻ ሳይሆን ስለ እግርኳስ ለማያውቁት በዙሪያችን ላሉ ሁሉ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ የምናሳውቅበት መንገድ ተመቻችቶልናል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ዝማሬዎችን ቤተሰቦቻችን፣ ጓደኞቻችን፣ የሥራ ባልደረቦቻችን እንዲያወቁና ዝማሬያችንን እንዲሰሙ የማድረጊያው መንገድ አግኝተናል፡፡ ከአፋችን የማይጠፉ ዝማሬዎቻችን ለስልኮቻችን ተዘጋጅተውልናል፡፡ ከዛሬ አንስቶ እኛ ብቻ ሳንሆን ስልኮቻችንም ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ይናገራሉ፤ ቅዱስ ጊዮርጊሳዊ መሆናችንን ይሰብካሉ፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስን ማራኪ ዝማሬዎች ይላበሳሉ፡፡ ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊ የሚደወሉ ጥሪዎች በሙሉ የቅዱስ ጊዮርጊስን ጉዞ፣ ውጣ ውረድ፣ ድል፣ ስኬት፣ ቤተሰባዊነት እና መሰል ኹነቶችን ለመስማት ይገደዳሉ፡፡ በቅድሚያ በሞባይል የስልክ የጽሑፍ መልዕከት መላኪያ ስፍራ ውስጥ እንግባ፡፡ በመቀጠል 822 ላይ “A” በማለት መልዕክት እንላክ፡፡ በመቀጠል ከ822 የCRBTተጠቃሚ መሆን መጀመራችንን የሚገልጽ የጽሑፍ መልዕክት ይደርሰናል፡፡ በመቀጠል የጥሪ ማሳመሪያ እንዲሆን የወደድነውን ዝማሬ ኮድ ብቻ ወደ 822 እንላክ፡፡ ከዚያም ከ822 የመረጥነው ዝማሬ የጥሪ ማሳመሪያ እንደሆነ ማረጋገጫ ይደርሰናል፡፡ ይህ ካልተሳካ ግን በድጋሚ የወደድነውን ዝማሬ ኮድ ብቻ ወደ 822 ለመላክ እንሞክር፡፡ ከእነዚህ ቅጽበቶች አንስቶ ወደ ስልካችን የሚደወሉ ስልኮች በሙሉ ...

3 West African players are on probation period in St George.

Image
It's known that St George gives chance to foreigner players. It is customary in St George to give chance to such players by making arrangements with agents. As many have become St George players through this process, others have failed to impress the coaches and went back home or left to another club. The 3 players from different African countries who are currently trying out have been doing their training with the U-20 team as St George was in Adigrat. Sources of Yeferesegnochu Gets / የፈረሰኞቹ ገጽ / confirmed these players are from Nigeria, Ghana and Mali.  As we were able to observe in today's training, these players were training with the main team. In the coming times, if they will be able to convince the coaches, they will be seen in St George jersey playing in 2nd EPL round and African Champions League .

3 የምዕራብ አፍሪካ ዜግነት ያላቸው ተጨዋቾች በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ውስጥ በሙከራ ላይ ይገኛሉ፡፡

Image
ቅዱስ ጊዮርጊስ ለተለያዩ የውጭ አገር ዜግነት ላላቸው ተጨዋቾች የሙከራ ዕድል እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ ከተለየዩ ወኪሎች ጋር ግንኙነቶችን በመፍጠር ተጨዋቾች የሙከራ ዕድል እንዲያገኙ ማድረግ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት የተለመደ አሰራር ነው፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ የሙከራ ጊዜያቸውን በተሳካ መንገድ በማለፍ ለክለቡ የፈረሙ ተጨዋቾች እንዳሉ ሁሉ ቁጥራቸው የበዛ የውጭ አገር ተጨዋቾች በሙከራ ጊዜያቸው አሰልጣኞቹን ማሳመን ባለመቻላቸው ምክንያት ወደ አገራቸው አሊያም በአገር ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ክለቦች እንዳቀኑ ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የሙከራ ዕድል የሰጣቸው 3 ተጨዋች ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ ተጨዋቾች ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አዲግራት በማቅናቱ ምክንያት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከ20 ዓመት በታች ስብስብ ጋር ልምምድ ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡ እነዚህ ተጨዋቾች ከናይጄሪያ፣ ጋና እና ማሊ ሀገራት የመጡ መሆኑን የፈረሰኞቹ ገጽ ምንጮች አረጋግጠውልናል፡፡ በዛሬው የልምምድ መርኃ ግብር ላይ ተገኝተን መመልከት እንደቻልነው እነዚህ ተጨዋቾች ከዋናው ቡድን ጋር ተቀላቅለው ልምምድ በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ በቀጣይ ከቡድኑ ጋር በሚኖራቸው ቆይታ ተገምግመው እንዲሁም አሰልጣኞቹን ማሳመን ከቻሉ በ2ኛ ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር እንዲሁም በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ላይ በቅዱስ ጊዮርጊስ ማሊያ የሚታዩ ይሆናል፡፡ በተቃራኒው አሰልጣኞቹን ማሳመን ካልቻሉ የሙከራ ጊዜያቸው ማብቃቱን ተከትሎ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የሚለያዩ ይሆናል፡፡

የቅዱስ ጊዮርጊስ የሴቶች ቡድን 2ኛ ተከታታይ ሽንፈትን አስተናግደዋል።

Image
ከ17 ዓመት የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ መልስ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሴቶች ቡድን ወደ ጨዋታ ተመልሰዋል፡፡  የ ዛሬ በ9 ሰዓት በተካሄደው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ አንደኛ ዲቪዝዮን 3ኛ ሳምንት ጨዋታ በሀዋሳ ከነማ 3—2 በሆነ ውጤት ሽንፈትን አስተናገደዋል። የቅዱስ ጊዮርጊስ ሴቶች ቡድን 10ኛ ደቂቃ ላይ ቤተልሄም ሰማን ባስቆጠረችው ጎል መሪ መሆን ቢችሉም፣ ሀዋሳ ከነማ በ14ኛ እና በ42ኛ ደቂቃ ላይ ባስቆጠሩት ጎል ታግዘው የመጀመሪያው አጋማሽ በሃዋሳ ከነማ 2—1 መሪነት ተጠናቋል።  በሁለተኛው አጋማሽ ጅማሬ በ46ኛ ደቂቃ ላይ ቤተልሄም ሰማን ለራሷም ሆነ ለክለቧ 2ኛ ጎል አስቆጥራ ጨዋታው በአቻ ውጤት እንዲቀጥል አስችላ ነበር። ሆኖም በ90ኛ ደቂቃ የሃዋሳ ከነማዋ የመስመር ተጨዋች 2 የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨዋቾችን በአስገራሚ ፍጥነት በማለፍ ወደ ሳጥን ውስጥ ያሻገረችውን ኳስ ሀዋሳዎች ወደ ጎልነት ቀይረው ሃዋሳ ከነማዎች ጨዋታውን 3–2 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል። የቅዱስ ጊዮርጊስ ሴቶች ቡድን በ2010 ዓ·ም የሴቶች የአንደኛ ዲቪዚዮን ውድድር 3 ጨዋታ አድርገዋል። ካለፉት 3 ጨዋታዎች ውስጥ በ2 ጨዋታዎች ሽንፈትን ሲያስተናግዱ በአንድ ጨዋታ ድል አድርገዋል። ሴት ፈረሰኞቻችን ሽንፈትን ያስተናገዱት በኢትዮ ኤሌክትሪክ እና በሀዋሳ ከነማ ሲሆን ማሸነፍ የቻሉት ጌድኦ ዲላን ነው። ባለፉት ጨዋታዎች ላይ 5 ጎሎችን ሲያስቆጥሩ 5 ጎሎችን አስተናግደዋል። በዚህም በጨዋታ በአማካይ 1·67 ጎል ሲያስቆጥሩ፣ 1.67 ጎሎችን አስተናግደዋል። ማራኪ የእግርኳስ ፍሰትን እየተገበ የሚገኘው የአሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ ስብስብ የእግርኳስ ቤተሰቡን የሚያስደስት እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል። ሴት ፈረሰኞቻችን በጥሩ የጨ...

የቀጥታ ስርጭት፦ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ

Image
(በወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የሚካሄደውን ይህ የኢትዮጵያ ፕሪሜየር ሊግ 8ኛ ሳምንት ጨዋታ ዋና ዋና እንቅስቃሴ በዚህ ሊንክ ላይ በኤዲት የምናካትት ይሆናል። የፈረሰኞቹ ገጽ ተከታታዮች ይህንን ሊንክ ሪፍሬሽ በማድረግ የጨዋታውን አበይት የየደቂቃ እንቅስቃሴዎች ማግኘት የምትችሉ ይሆናል።) ******** አጠቃላይ ውጤት:— ወልዋሎ አዲግራት የኒቨርስቲ 0-0 ቅዱስ ጊዮርጊስ ******** ጨዋታውን ለመጀመር ሁለቱም ቡድኖች ወደ ሜዳ ገብተዋል። 1‘  ጨዋታው በወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ኳስ ጀማሪነት ተጀምሯል። 2‘ የቀድሞ የፈረሰኞቹ የግራ መስመር አጥቂ ፕሪንስ ሰርቪንዮ የቀድሞ ክለቡን እየገጠመ ይገኛል። 4‘ ክለባቸውን ለመደገፍ ከአዲስ አበባ በተለያዩ የትራንስፓርት አማራጮች የተጓዙት የፈረሰኞቹ ደጋፊዎች በአዲስ አበባ ስታዲየም አጠራር በካታንጋ አከባቢ በመቀመጥ ክለባቸውን እያበረታቱ ይገኛሉ። 6‘ ምንተስኖት አዳነ በዛሬው ጨዋታ ፈረሰኞቹን በአንበልነት እየመራ ወደ ሜዳ ገብቷል። 8‘ ፕሪንስ ሰርቪኒዮ በመልሶ ማጥቃት ያገኘውን ኳስ በቀጥታ ወደ ጎል ቢመታውም በሮበርት ኦዶንካራ በቀላሉ ተይዟል። 10‘ አቡበከር ሳኒ ከመስመር ወደ ሳጥን ያሻገረውን ጥሩ ኳስ ምንተስኖት አዳነ ወደ ጎል ቢመታውም በግብ ጠባቂው ተይዞበታል። 12‘ ምንም እንኳን የጨዋታው ሜዳ ለጨዋታ አመቺ ባይሆንም ፈረሰኞቹ ኳስን ተቆጣጥረው ወደ ግብ ክልል ለመድረስ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ። 14‘ አበባው ቡጣቆ ከሜዳው በስተግራ የተገኘውን ቅጣት ምት ወደ ጎል አሻምቶ ሳላሃዲን በርጌቾ በጭንቅላቱ ለመግጨት ቢሞክርም የመሃል ዳኛው ግብ ጠባቂው ላይ ጥፋት ተሰርቷል ብለው ጨዋታው በቅጣት ምት ቀጥ...

It's Matchday!

Image
There is not much region in Ethiopia where St George fans have not been. They have been following their great club, be it to the North, South, East or West. The have waved St George’s flag high in parts of Ethiopia. They have toured Ethiopia talking and singing about St George wearing beautiful St George jersies. We don’t think we are mistakie። when we say it is the furthest in Ethiopian Premier League trip history. This city established in 1818GC is the next city to be decorated by St George fans. St George fans who don’t back down for distance, weather changes and different states are on the move to Adigrat since the past few days. Adigrat, on top of the usual yellow, will be decorated with colours of St George - yellow, red and orange. And will be like a painting made by a great artist. And will host the club that leads by far in Ethiopian football. The city habitants will meet St George and its fans, who they were only hearing about. St George is not a club who tra...

ዛሬ የጨዋታ ቀን ነው!

Image
የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ያልረገጡት ክልል ውስን ነው፡፡ ያልሄዱበት የኢትዮጵያ መዳረሻዎች ጥቂት ናቸው፡፡ በሰሜን ቢባል በደቡብ፣ በምስራቅ ቢባል በምዕራብ ታላቁን ክለባቸው ተከትለው ተጉዘዋል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ አርማን ከፍ አድርገው በተለያዩ የኢትዮጵያ አከባቢዎች ላይ አሷይተዋል፡፡ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ እየዘመሩ፣ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ እየወጉ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ውብ አርማዎችን ለብሰው ኢትዮጵያን ዞረዋል፡፡ አዲግራት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጉዞ ታሪክ ከአዲስ አበባ የራቀ ቦታ ላይ ያለች ከተማ ናት ብንል የተሳሳትን አይመስለንም፡፡ ይህች ምስረታዋን በ1811 ዓ.ም ያደረገችው ከተማ ዛሬ በቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ልትደምቅ የተመረጠች ከተማ ሆናለች፡፡ የቦታ ርቀት፣ አየር ጸባይ ለውጥ፣ ነባራዊ ሁኔታ እና መሰል እንቅፋቶች ወደ ኋላ የማይመልሳቸው የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ካለፉት ጥቂት ቀናት አንስቶ ወደ ስፍራው በማቅናት ላይ ይገኛሉ፡፡ አዲግራት ከለመደችው ቢጫ ቀለም በተለየ በዛሬው ዕለት የቅዱስ ጊዮርጊስ ቀለማት በሆኑት ቢጫ፣ ቀይ እና ብርቱካንማ ቀለማት ትቀልማለች፡፡ በጥሩ ሰዓሊ እንደተሳለ ስዕል ደምቃ ትታያለች፡፡ የኢትዮጵያ እግርኳስን በሰፊ ርቀት የሚመራውን ክለብ ታስተናግዳለች፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲባል ስሙን ከሩቅ ሲሰሙ የነበሩት የከተማው ነዋሪዎች ክለባችንን እና ደጋፋዎቹን ይተዋወቃሉ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ክልል ስታዲየም የሚያቀናው ለመርኃ ግብር ማሟያነት አይደለም፡፡ ለመርኃ ግብር ማሟያነት የሚጫወት ክለብ ቢሆን ኖሮ ደጋፊዎቹ 900 ኪሎ ሜትሮችን አቋርጠው ባልተጓዙ ነበር፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ የክልል ስታዲየም ፎቢያ የለበትም፡፡ ይህንን ጠንቅቀው የሚያውቁ ደጋፊዎቹ ክለባቸውን በፍጹም ብቻውን ለመተው አይሞክሩምና 900 ...

Match Preview:- Welwalo Adigrat University Vs St George

Image
Ethiopian Premier League 8th week matches will be played at Addis Ababa and regional city stadiums. St George delegates left for Adigrat yesterday. St George Vs Welwalo Adigrat University will take place at Adigrat stadium with a kick off 3:00 pm. Welwalo Adigrat University from Higher League to Premier League! Welwalo Adigrat University in 2016/17 was participating in the North part in Ethiopian Higher League. In the end of the last season, Welalo Adigrat University joined the Premier League winning the zone. The club, although losing to Jimma 1Kenema at Diredawa, they joined the Premier League finishing 2nd at last. We remember it was Aklecias Girma who scored a penalty at the 22nd minute when Jimma Kenema won the League tittle. Welwalo Adigrat University was strengthening the team after joining the premier league by making 10 signings. Mulualem Tilahun, Robel Girma, Bereket Tesema, Biniam Ayele, Eyub WeldeMariam, Wegderes Taye, Biruk Ayele, Enyew Kassahun, Tesfaye ...

የቅድመ ጨዋታ ዳሠሳ፦ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከቅዱስ ጊዮርጊስ

Image
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 8 ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከዛሬ ( ቅዳሜ ) አንስቶ በክልል እና በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳሉ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሊጉን የ 8 ኛ ሳምንት ጨዋታ ወደ አዲግራት ተጉዞ ለማከናወን የብድኑ የልዑካን ቡድን አባላት በትላንትናው ዕለት ወደ አዲግራት አቅንተዋል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ እሁድ በ9 ሰዓት በአዲግራት ስታዲየም የሚካሄድ ይሆናል፡፡ የወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጉዞ ከከፍተኛ ሊግ እስከ ፕሪሚየር ሊግ ! ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በ 2009 ዓ . ም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር ውስጥ በሰሜን ዞን ምድብ ሲወዳደር የቆየ ክለብ ነው፡፡ እጅግ አድካሚ በሆነው የከፍተኛ ሊግ ውድድር ላይ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የዞኑ ሻምፒዮን በመሆን ወደ ፕሪሚየር ሊግ ያደገው ባሳለፍነው ዓመት መገባደጃ ላይ ነበር፡፡ ይህ ቡድን የከፍተኛ ሊጉ አሸናፊ ለመሆን በድሬዳዋ ስታዲየም ከጅማ ከነማ ጋር ባደረገው ጨዋታ ድል ሳይቀናው ቀርቶ በአጠቃላይ በከፍተኛ ሊጉ 2ኛ ሆኖ ማጠናቀቅ ችሏል፡፡ በፍጻሜው ጨዋታ የጅማ ከነማው ተጨዋች አቅሌስያስ ግርማ በ22ኛ ደቂቃ ላይ ባስቆጠረው የፍጹም ቅጣት ምት ጎል ጅማ ከነማ የከፍተኛ ሊጉ ሻምፒዮን መሆኑ ይታወሳል፡፡ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ከመጣ ጀምሮ ቡድኑን ለማጠናከር ተንቀሳቅሷል፡፡ ይህ ክለብ ከ10 በላይ አዲስ ተጨዋቾችን በማስፈረም ቡድኑን እንደ አዲስ በመገንባት ላይ የቆየ ክለብ ነው፡፡ ሙሉዓለም ጥላሁን፣ ሮቤል ግርማ፣ በረከት ተሰማ፣ ቢኒያም አየለ፣ እዩብ ወልደማ...