ማሊያዊው የፊት እና የመስመር አጥቂ አማራ ማሌ አዲሱ ፈረሰኛ ለመሆን ተቃርቧል።
አማራ ማሌ በማሊ እግርኳስ ክለብ ታሪክ ታላላቅ ስም ባላቸው ክለቦች ውስጥ ያለፈ ተጨዋች ነው። በአሁኑ ወቅት በማሊ ታላቅ ክለብ የሆነው የስታድ ማሊ ክለብ ተጨዋች ሲሆን 1ሜትር ከ82 ሳንቲሜትር ይረዝማል። ይህ ተጨዋች በማሊ ዋና ከተማ ባማኮ ታህሳስ 5 ቀን 1982 እንደተወለደ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። ተጨዋቹ 25 ዓመቱ ሲሆን በሁለቱም እግሮቹ ኳስ መጫወት የሚችል ተጨዋች ነው፡፡
በአ
ከ2009-2012
የማሊ ክለብ ለሆነው ባማኮ፣ 2013-2015 ለጆሊባ እንዲሁም በ2016 ወደ ጊኒ ተጉዞ ለሆሪያ ክለብ መጫወት ችሏል፡፡ ከሆሪያ ክለብ ጋር ከተለያየ አንስቶ ለስታድ ማሊ
እየተጫወተ ይገኛል፡፡ ይህ ተጨዋች በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ 2 ጨዋታዎች ላይ፣ በካፍ ኮንፌደሬሽን ካፕ 2 ጨዋታዎች ላይ፣ ከ20 አመት በታች የአለም ዋንጫ ላይ 2 ጨዋታዎች ላይ፣ በቻን የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ላይ 1 ጨዋታዎች ላይ፣ በቻን የአፍሪካ ዋንጫ 3 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቷል፡፡ ተጨዋቹ በ2016 የጊኒ ክለብ የሆነው ሆሪያ በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ የዛምቢያውን ዜስኮ ዩናይትድን ሲገጥም 65 ደቂቃዎችን ያህል ተሰልፎ ተጫውቷል፡፡
አማራ
ማሌ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የተያያዘ ታሪክ ያለው ተጨዋች ነው፡፡ በ2013 ቅዱስ ጊዮርጊስ በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ጆሊባን ሲገጥም ይህ ተጨዋች በወቅቱ የጆሊባ ተጨዋች ሆኖ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገጥሟል፡፡ በዚያ ጨዋታ ላይ በ78ኛ ደቂቃ ተቀይሮ ገብቶ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ተጫውቷል፡፡ በወቅቱ ይህ ጨዋታ በማሊ የተከናወነ ሲሆን ጨዋታው 1-1 በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
አማራ
ማሌ ከ3 ዓመታት በፊት የነበረውን የእግርኳስ እንቅስቃሴ ከታች ባለው ቪዲዮ ላይ ተካቷል፡፡
Comments
Post a Comment