Posts

Showing posts from March, 2018

በሚዲያ አጠቃቀም የኋልዮሽ ጉዞ ላይ ያለው ቅዱስ ጊዮርጊስ!

Image
ቅዱስ ጊዮርጊስ በአህጉራዊ ውድድሮች ላይ ውጤት በማምጣት ጭምር እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ ባሳለፍነው ዓመት ከአፍሪካ ታላላቅ ክለቦች ጋር ጨዋታዎችን ማድረግ ችለናል፡፡ ከታላላቅ ክለቦች ጋር ስንጫወት ከእግር ኳሱ ጎን ለጎን የምንቀስማቸው አስተዳደራዊ እና መሰል ተግባራት ሊኖሩ ይገባል፡፡ ባሳለፍነው ዓመት ቅዱስ ጊዮርጊስ በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ የምድብ ድልድል ውስጥ ገብቶ ጨዋታዎችን ሲያደርግ የነበረው የሚዲያ አጠቃቀም ደካማ ነበር፡፡ ሆኖም የፈረሰኞቹ ገጽ በዚያ ወቅት አንድም ነገር ለመናገር አልወደድንም ነበር፡፡ ምክንያታችን የነበረው ለውድድሩ እንግዳ ከመሆን የመነጨ ነው በሚል ነበር፡፡ ይህ ከያዝነው ውድድር ዓመት አንስቶ ይስተካከላል ብለን ተስፋ አድርገን ነበር፡፡ ሆኖም ግምታችን ትክክል አልነበረም፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዛሬም በሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ እጅግ ደካማ ክለብ መሆኑን በተግባር እያሳየ ይገኛል፡፡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ምስረታ ከረጅም አመት በኋላ የተመሰረቱ ክለቦች ከቅዱስ ጊዮርጊስ የተሻለ ሲንቀሳቀሱ እየታዘብን እንገኛለን፡፡ በምስራቅ አፍሪካ ያሉ ብዙም በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ የመሳተፍ ታሪክ የሌላቸው ክለቦች ከቅዱስ ጊዮርጊስ እንደሚሻሉ እያየን ነው፡፡ ለዚህም ማሳያዎችን እንጥቀስ፡፡ 1. የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ይፋዊ ድረ ገጽ! ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተወሰኑ ዓመታት በፊት የራሱን ድረ ገጽ ከፍቶ መረጃዎችን ያስተላልፍ ነበር፡፡ ምንም እንኳ ድረ ገጹ ዘመናዊነት ያልተከተለ ቢሆንም ጥረቶቹ ግን የሚያበረታቱ ነበሩ፡፡ ይህ ድረ ገጽ አሁን ላይ አገልግሎት አይሰጥም፡፡ ከዓመታት በፊት የተሰጡትን መረጃዎች ይዞ ተቀምጧል፡፡ በአሁን ሰዓት የድረ ገጹ የደረጃ ሰንጠረዥ ማሳያ እያሳየው የሚገኘው የ2008 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የደረጃ

It's Match day!

Image
"Its challengers terrified Its fame gets it respected Its heroism cannot be denied Nothing more gets one pleased” It is still us representing Ethiopia in Africa's great football tournament. It is St George that is waving Ethiopia's flag high. It is the Horsemen that are prevail to pair their club's flag with the Ethiopian flag. It was our St George that was in the good and bad times with Ethiopia since establishment. And so Wednesday came. The day that was long awaited in the hearts of all St George fans has arrived. The day that was being countdown is here. The nights and days that didn't seem to end are gone. And the long Tuesday night is finally dawn and is match day. On such days, children are beautified by St George colors. Youths get up from their sleepless beds bearing the hope in their hearts to make St George great in Africa. Elder lies that are libraries of St George put on their hats of "V" and March to stadium. They le

የፈረሰኞቹ ገጽ - ዛሬ የጨዋታ ቀን ነው!

Image
«የሚገጥሙት ይፈሩታል፣ ዝና ሰምተው ያከብሩታል፤ ጀግንነቱን ያምኑለታል፣ ከዚህ በላይ ደስታ የታል?» ዘንድሮም በታላቁ የአፍሪካ እግር ኳስ ውድድር ላይ ኢትዮጵያ እየወከልን ያለነው እኛ ነን፡፡ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ከፍ አድርጎ ይዞ የተገኘነው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነው፡፡ የክለባችንን አርማ ከኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ጋር አጣምረው ይዘው የመገኘት ብቃቱን ያገኙት ፈረሰኞቹ ናቸው፡፡ ከምስረታው አንስቶ ከኢትዮጵያ ጎን ያልተለየ፣ በኢትዮጵያ የመከራ ጊዜም ሆነ የድል ጊዜ ከጎን የተገኘው የእኛ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነው፡፡ እንሆ ረቡዕ ሆነ። በሁሉም የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊ ልብ ውስጥ ሲናፈቅ የከረመው ቀን ደረሰ። ቁልቁል ቀን ሲቆጠርለት የነበረው የጨዋታ ቀን ተገኘ። የሚነጋ የማይመስሉ ለሊቶች፣ የማያልቅ የሚመስሉ ቀናቶች አልፈው፣ የማክሰኞ ረጅም ለሊት ተጠናቆ የጨዋታ ቀን ላይ ተገኘን። በእንዲህ አይነት ቀን ህፃናት በቅዱስ ጊዮርጊስ ቀለማት ይዋባሉ። የወጣቶቹ ልብ ቅዱስ ጊዮርጊስን በአፍሪካ አህጉር ታላቅ የማድረግ ህልማቸውን ይዘው ካልተኙበት መኝታቸው ላይ ይነሳሉ። የቅዱስ ጊዮርጊስ የታሪክ መዝገብ የሆኑት አረጋውያን በ "V" ምልክት የደመቀውን ኮፍያቸውን አደርገው በማለዳ ጉዟቸውን ወደ ካምቦሎጆ ያደርጋሉ። እስካርፓቸውን በአንገታቸው፣ አርማቸውን በእጃቸው ይዘው ከቤት ይወጣሉ። ለሁላችንም ቀኑን በጉጉት ለጠበቅን፣ ይህንን ቀን ለናፈቅን ሁሉ ዛሬ የጨዋታ ቀን ነው!!! ዛሬ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ጊዮርጊስ በአዲስ አበባ የሚነግስበት ቀን ነው። በአፍሪካ ታላቁ የውድድር መድረክ ላይ የሚታይበት ዕለት ነው። ዛሬ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቀን ነው። በመላው የስታዲየሙ ክፍሎች የሻምፒዮኖቹ ደጀኖች ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ታላቅነቱ ያዜማሉ። የዛሬ ዝማሪያ