የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 11 ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከነገ አንስቶ በክልል እና በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳሉ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ የዚህ ሳምንት መርኃ ግብሩን የሚያከናውነው በወልድያው ሼህ መሐመድ ሁሴን አል አሙዲ ስታዲየም ሲሆን ተጋጣሚው ወልድያ ስፖርት ክለብ ነው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወልድያ ስፖርት ክለብ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ አርብ በ 9 ሰዓት ይ ካሄዳል፡፡ ወልድያ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ያሳለፍነው ዓመት እርስ በእርስ ግንኙነት! በ 2009 ዓ . ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለቱ ቡድኖች የመጀመሪያ ዙር ጨዋታቸውን ያደረጉት ረቡዕ ጥር 3 ቀን 2009 ዓ . ም ነበር። ይህ ጨዋታ ምሽት 11፡30 የተካሄደ ጨዋታ ሲሆን የዚህ ጨዋታ አሸናፊ የሆነው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነው፡፡ በዚህ ጨዋታ ፈረሰኞቹ ጎል ለማስቆጠር 75 ያህል ደቂቃዎችን ለመጠበቅ ተገደው ነበር፡፡ በጨዋታው 75ኛ ደቂቃ ላይ ሳላሃዲን ሰኢድ የፍጹም ቅጣት ምት መግቢያ ላይ ያገኘውን ኳስ ለአቡበከር ሳኒ ሰጥቶት አቡበከር ሳኒ ከፍጹም ቅጣት ምት ክልል ውጪ መሬት ለመሬት ኳሱን አክርሮ በመምታት የጨዋታውን ብቸኛ ጎል ማስቆጠሩ ይታወሳል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ የ 2009 ዓ . ም የ 2 ኛ ዙር ጨዋታውን ከወልድያ ጋር ያደረገው ረቡዕ ሚያዚያ 18 ቀን 2009 ዓ . ም ነበር፡፡ ይህ ጨዋታ የተካሄደው በወልድያ ስፖርት ክለብ በሼህ መሐመድ አል አሙዲ ስታዲየም ሲሆን የዚህ ጨዋታ ውጤት ለቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አስፈላጊ ውጤት ነበር፡፡ ለዚህም እጅግ በርካታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ወደ ስፍራው ማቅናታቸው ይታወሳል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች በ8 አውቶብሶች፣ በግል ትራንስፖርት እና በአየር ወደ ስ
Comments
Post a Comment