የቅዱስ ጊዮርጊስ የመስመር አጥቂ ተጨዋች ጋዲሳ መብራቴ ጉዳት አስተናገደ!



ጋዲሳ መብራቴ ቅዱስ ጊዮርጊስን የተቀላቀለው በያዝነው የውድድር ዓመት ሲሆን በአሰልጣኝ ቫዝ ፒንቶ በሚመራው ቡድን ውስጥ የቋሚ ተሰላፊነት ዕድል ያገኘ ተጨዋች ነው። ይህ ተጨዋች ቅዱስ ጊዮርጊስ በ2010 ዓ·ም ባደረጋቸው የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ላይ በተደጋጋሚ መሰለፍ ችሏል። 


ጋዲሳ መብራቴ ፈረሰኞቹ ከጅማ አባ ቡና ጨዋታ አስቀድሞ በነበራቸው የመጨረሻ ልምምድ ላይ ጉዳት አስተናግዷል። በዚህ የልምምድ መርኃ ግብር ላይ የተሳተፈው ጋዲሳ የልምምዱ መገባደጃ ላይ 
የጡንቻ መሸማቀቅ (Hamstring) ጉዳት አስተናግዷል። ተጨዋቹ ይህን ጉዳት ካስተጋናደ በኋላ በስፍራው በሚገኙ የህክምና ባለሙያዎች የህክምና እርዳታ ተሰጥቶታል። በመሆኑም ተጨዋቹ ካስተናገደው ጉዳት አንፃር በነገው ዕለት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጅማ አባ ጅፋር ጋር የሚያደርጉት የጨዋታ አካል ይሆናል ተብሎ አይጠበቀም። በዚህም መሰረት ቅዱስ ጊዮርጊስ በነገው ዕለት በጉዳት እና ህመም ምክንያት የማይጠቀማቸው ተጨዋቾች ቁጥር 6 ደርሷል።

Comments

Popular posts from this blog

ጅማ - ደማችን የፈሰሰባት፣ ድላችንን የተቀማንባት ከተማ!

በሚዲያ አጠቃቀም የኋልዮሽ ጉዞ ላይ ያለው ቅዱስ ጊዮርጊስ!

በፖለቲካ የተዋጠው፣ የፖለቲከኞች እጅ የተጫነው እግርኳሳችን! - በፈረሰኞቹ ገጽ