የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ድንቅ ዝማሬዎች በሚስማር ተራ! Get link Facebook X Pinterest Email Other Apps - January 01, 2018 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመከላከያ ጋር ተጫውቶ 0-0 በተለያበት ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች በተለምዶ ሚስማር ተራ በሚባለው ስፍራ የነበራቸው ድንቅ ዝማሬ እና ድጋፍ! Get link Facebook X Pinterest Email Other Apps Comments
ጨዋነታችንን ዘመናት አይዋጁትም፤ ሁኔታዎች አይቀይሩትም! - February 21, 2018 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአዳማ ከነማ ጋር ካደረገው ጨዋታ አንስቶ በተፈጠሩ ሁኔታዎች የተለያዩ አስተያየቶችን እየተመለከትን እንገኛለን፡፡ ከጋዜጠኞች፣ ከደጋፊዎች እና መሰል የእግርኳሱ ባለድርሻ አካላት የተለያዩ አስተያቶች ሲሰነዘሩ ተመልክተናል፡፡ ለመደመጥ የሚበቁ፣ ለማድመጥ የሞከርናቸው እና ለአቅመ መደመጥ የማይበቁ የተለያዩ አስተያየቶችን ስናደምጥ ሰነበትን፡፡ እነዚህን ተንተርሰን የፈረሰኞቹ ገጽ አዘጋጆች የምናምንበትን ኃሳቦች ለመሰንዘር ተገደድን፡፡ በወቅቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአዳማ ከነማ አቻ በተለያየበት ጨዋታ ላይ የተነሳውን ተቃውሞና መሰል ድርጊቶች የፈረሰኞቹ ገጽ ተገቢ እንዳልሆነ እና ይህ በቀጣይ መደገም እንደሌለበት አንስተን ጽፈናል፡፡ እኛ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ይህንን ድርጊት ተንተርሰው መታረም ያለበትን ነጥብ መሆኑን በማንሳት የድርጊቱን ትክክል አለመሆን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ያለ ማንም ቀስቃሽ ድርጊቱን በይፋ አውግዘው ይቅርታ ሲጠይቁ ተመልክተናል፡፡ የተለያዩ መድረክ ያገኙም ደጋፊዎች ድርጊቱን አንስተው ተወያይተዋል፡፡ የፈረሰኞቹ ገጽ ትኩረትን የሳቡት በተለያዩ የራዲዮ እና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ ይህንን ድርጊት ተንተርሶ እየተሰሩ ያሉ ፕሮግራሞች ናቸው፡፡ ምንም እንኳ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ሳይቀር ለግበአትነት መዋል የሚችሉ ፕሮግራሞች እንዳሉ መናገር ባንክድም ይህንን ድርጊት ተንተርሰው ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብን የማጥላላት፣ ደጋፊውን የማሳነስ፣ ድጋፉን የማንቋሸሽ እና መሰል ስም ማጥፋቶች ሲሰነዘሩ የተመለከትናቸው የቴሌቪዥንም ሆነ የራዲዮ ፕሮግራሞች አሉ፡፡ ወቀሳ ጥሩ ነው፡፡ ትችት መልካም ነው፡፡ ሆኖም ወቀሳም ሆነ ትችት ዕውቀት ሊላበሱ እና ለተወቃሹ አካል መማሪያ ነ... Read more
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከደደቢት - የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች አስደናቂ ዝማሬዎች! - February 26, 2018 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከደደቢት ጋር ተጫውቶ 0-0 በተለያየበት ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ድባብ እና ደማቅ ህብረ ዝማሬ የፈረሰኞቹ ገጽ ባስቀረው ቪዲዮ ይህንን ይመስላል። Read more
ትውስታ - በ2017 የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ የቅዱስ ጊዮርጊስ ጉዞ - ክፍል 3 (የመጨረሻ ክፍል) - February 08, 2018 የ2018 የቶታል ካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ የክለቦች ውድድር በያዝነው ሳምንት መገባደጃ ላይ ይጀመራል፡፡ በዚህ ውድድር ለተከታታይ 4 አመታት ኢትዮጵያን በመወከል ክለባችን ቅዱስ ጊዮርጊስ ይሳተፋል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባሳለፍነው ዓመት በኢትዮጵያ የክለቦች ታሪክ በአፍሪካ ሻምዮንስ ሊግ የምድብ ድልድል ውስጥ የገባ የመጀመሪያው ኢትዮጵያ ክለብ መሆኑ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም የዘንድሮው የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ መጀመርን ተንተርሰን ያሳለፍነው ዓመት ቅዱስ ጊዮርጊስ ጉዞን እያነሳሳን እንገኛለን፡፡ ባለፉት ቀናት በክፍል አንድ እና ሁለት ምልከታችን ቅዱስ ጊዮርጊስ የ2017 የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ የቅድመ ማጣሪያ፣ የ1ኛ ዙር እና የምድቡ የመጀመሪያ 3 ጨዋታዎችን ማነሳሳታችን ይታወሳል፡፡ ለዛሬ በክፍል 3 እና በመጨረሻ ክፍል ያዘጋጀነው ጽሑፍ ይህንን ይመስላል፡፡ ኤኤስ ቪታ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ይህ ጨዋታ የ2017 የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ 4ኛ ጨዋታ ሆኖ ተከናውኗል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ እስከዚህ ጨዋታ ድረስ 9 ጎል አስቆጥሮ ምንም ጎል አላስተናገደም፡፡ የተጋጣሚዎቹን መረብ 9 ጊዜ ጎብኝቶ የራሱን መረብ በሚገባ ከጥቃት ጠብቆ ቆይቷል፡፡ ከታላላቆቹ ማሜሎዲ ሰንዳውንስ እና ኤስፔራንስ ደ ቱኒዝ ጋር ጨዋታውን አድርጎ ጎሉን አላስደፈረም፡፡ በዚህም የተከላካይ ክፍሉ ጥንካሬ በግልጽ ታይቷል፡፡ የመሃል ተከላካዮቹን አስቻለው ታመነን እና ሳላሃዲን በርጌቾን በምርጥ 11 የካፍ ስብስብ ውስጥ አስገብቷል፡፡ በሌላ በኩል አሰልጣኝ ማርት ኖይ ወደ ክለቡ እንደማይመለሱ እርግጥ ሆኗል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ የቦርድ አመራሮች ስብሰባ አድርገው ምክትል አስልጣኞቹ ፋሲል ተካልኝ እና ዘሪሁን ሽንገታ ክለቡን ይዘው እንዲቀጥሉ ውሳኔ አሳለፉ፡፡ በዚህም ፈረሰኞቹ በምክትል አሰልጣኞቹ እየተመሩ ወደ... Read more
Comments
Post a Comment