ጨዋነታችንን ዘመናት አይዋጁትም፤ ሁኔታዎች አይቀይሩትም!
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአዳማ ከነማ ጋር ካደረገው ጨዋታ አንስቶ በተፈጠሩ ሁኔታዎች የተለያዩ አስተያየቶችን እየተመለከትን እንገኛለን፡፡ ከጋዜጠኞች፣ ከደጋፊዎች እና መሰል የእግርኳሱ ባለድርሻ አካላት የተለያዩ አስተያቶች ሲሰነዘሩ ተመልክተናል፡፡ ለመደመጥ የሚበቁ፣ ለማድመጥ የሞከርናቸው እና ለአቅመ መደመጥ የማይበቁ የተለያዩ አስተያየቶችን ስናደምጥ ሰነበትን፡፡ እነዚህን ተንተርሰን የፈረሰኞቹ ገጽ አዘጋጆች የምናምንበትን ኃሳቦች ለመሰንዘር ተገደድን፡፡ በወቅቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአዳማ ከነማ አቻ በተለያየበት ጨዋታ ላይ የተነሳውን ተቃውሞና መሰል ድርጊቶች የፈረሰኞቹ ገጽ ተገቢ እንዳልሆነ እና ይህ በቀጣይ መደገም እንደሌለበት አንስተን ጽፈናል፡፡ እኛ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ይህንን ድርጊት ተንተርሰው መታረም ያለበትን ነጥብ መሆኑን በማንሳት የድርጊቱን ትክክል አለመሆን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ያለ ማንም ቀስቃሽ ድርጊቱን በይፋ አውግዘው ይቅርታ ሲጠይቁ ተመልክተናል፡፡ የተለያዩ መድረክ ያገኙም ደጋፊዎች ድርጊቱን አንስተው ተወያይተዋል፡፡ የፈረሰኞቹ ገጽ ትኩረትን የሳቡት በተለያዩ የራዲዮ እና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ ይህንን ድርጊት ተንተርሶ እየተሰሩ ያሉ ፕሮግራሞች ናቸው፡፡ ምንም እንኳ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ሳይቀር ለግበአትነት መዋል የሚችሉ ፕሮግራሞች እንዳሉ መናገር ባንክድም ይህንን ድርጊት ተንተርሰው ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብን የማጥላላት፣ ደጋፊውን የማሳነስ፣ ድጋፉን የማንቋሸሽ እና መሰል ስም ማጥፋቶች ሲሰነዘሩ የተመለከትናቸው የቴሌቪዥንም ሆነ የራዲዮ ፕሮግራሞች አሉ፡፡ ወቀሳ ጥሩ ነው፡፡ ትችት መልካም ነው፡፡ ሆኖም ወቀሳም ሆነ ትችት ዕውቀት ሊላበሱ እና ለተወቃሹ አካል መማሪያ ነ...


Comments
Post a Comment